Thursday, February 22, 2024

 

በተሻሻለው የፌደራል የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/92 መሰረት ከጋብቻ ውጭ እንደባልና ሚስት ስለመኖሩ የሚቀርብ ማስረጃ
ከጋብቻ ውጭ እንደባልና ሚስት መኖር ሴቲቱ እና ወንዱ ጋብቻ ሳይፈጽሙ በጋራ እንደባልና ሚስት መኖር በመጀመራቸው ብቻ የሚመሰረት ነው።
ይህን ግንኙነት ማስረዳት የሚቻለውም በአንቀጽ 106 /1/ እና /2/ እንደተመለከተው የግንኙነቱን መኖር በማስረዳት ሲሆን ይህ ግንኙነት አለ የሚባለውም ሁለቱ በህግ የተጋቡ ባይሆንም የተጋቡ ሰዎችን ሁኔታ የሚያሳዩና በቤተዘመድ እና በማህበረሰቡም እንደተጋቡ ሰዎች የሚኖሩ ናቸው ተብለው ሲገመቱ ነው። ይህ ማስረጃ ከቀረበም እንደባልና ሚስት አብረው የሚኖሩ ናቸው ተብሎ የህግ ግምት የሚወሰድ ሲሆን ግምቱንም ግንኙነቱ አለመኖሩን ማስረጃ አቅርቦ በማስረዳት ማስተባበልና ማፍረስ ይቻላል።
በሰበር መዝገብ ቁጥሮች 50580/ቅጽ 11/፥ 96853/ቅጽ 18/፥ 126411/ቅጽ 22/ የተሰጡ ትርጉሞቸን ለበለጠ ግንዛቤ ማንበብ ይችላሉ።
Endalamaw Alelign/LLM, LLB/
Attorney and Legal Consultat
0912771896

No comments:

Post a Comment

  ያልተጠየቀ ዳኝነት አይሰጥም፤ በግልጽ ያልተሰጠ ፍርድም አይፈጸምም። መሰረታዊው የፍትሐብሔር ክርክር አመራር መርህ በግልጽ ያልተጠየቀ ዳኝነት አይሰጥም የሚል ነው። ይህም ስለፍርድ በሚያትተው የፍትሀብሄር ሥነ-ሥርዓት ህጉ...