በተሻሻለው የፌደራል የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/92 መሰረት ከጋብቻ ውጭ እንደባልና ሚስት ስለመኖሩ የሚቀርብ ማስረጃ
ከጋብቻ ውጭ እንደባልና ሚስት መኖር ሴቲቱ እና ወንዱ ጋብቻ ሳይፈጽሙ በጋራ እንደባልና ሚስት መኖር በመጀመራቸው ብቻ የሚመሰረት ነው።
ይህን ግንኙነት ማስረዳት የሚቻለውም በአንቀጽ 106 /1/ እና /2/ እንደተመለከተው የግንኙነቱን መኖር በማስረዳት ሲሆን ይህ ግንኙነት አለ የሚባለውም ሁለቱ በህግ የተጋቡ ባይሆንም የተጋቡ ሰዎችን ሁኔታ የሚያሳዩና በቤተዘመድ እና በማህበረሰቡም እንደተጋቡ ሰዎች የሚኖሩ ናቸው ተብለው ሲገመቱ ነው። ይህ ማስረጃ ከቀረበም እንደባልና ሚስት አብረው የሚኖሩ ናቸው ተብሎ የህግ ግምት የሚወሰድ ሲሆን ግምቱንም ግንኙነቱ አለመኖሩን ማስረጃ አቅርቦ በማስረዳት ማስተባበልና ማፍረስ ይቻላል።
Endalamaw Alelign/LLM, LLB/
Attorney and Legal Consultat
0912771896
No comments:
Post a Comment